Horn Magazine
Thursday, May 15, 2025
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
Horn Magazine
No Result
View All Result

Home » በተመሳሳይ የነፍስ ማጥፋት ወንጀል የተከሰሰው ጥቁር አሜሪካዊ 12 አመት ሲፈረድበት ነጯ ፖሊስ ኪም ሁለት አመት ተፈረደባት!

በተመሳሳይ የነፍስ ማጥፋት ወንጀል የተከሰሰው ጥቁር አሜሪካዊ 12 አመት ሲፈረድበት ነጯ ፖሊስ ኪም ሁለት አመት ተፈረደባት!

July 8, 2022
in ብሔራዊ
1 min read
Black Cop Mohamed Noor- Kim Potter
ShareSharePin

እ.ኤ.አ ሚያዝያ 11/ 2021 የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ኦፊሰር ኪም ፖተር ዳኡንት ራይት የተባለውን የሀያ አመት ወጣት የትራፊክ መኪና ማቆምያ ጋር ተኩሳ ገላዋለች። የዚህን የ 20 አመት ጥቁር አሜሪካዊ ወጣት ህይወት በመቅጠፏ ባለፈው ሳምንት ለሁለት አመታት ብቻ በእስር እንድትቆይ ተፈርዶባታል። በሚያስገርም ሁኔታ የቀድሞ የሚኒያፖሊስ ጥቁር ሱማሌ-አሜሪካዊ የፖሊስ ኦፊሰር የሆነው ሙሐመድ ኑር በ ሀምሌ 15/2017 ላይ ጀስቲን ሩስዝይክን ተኩሶ በመግደሉ የ 12 አመት የእስር ቅጣት ተጥሎበታል። ነጣ ያለ ቢጫ ቀለም ጸጉር የነበራት ጀስቲን ከዳኡንት ጋርም ይሁን በተለምዶ ከሚታወቁ የፖሊስ ተጎጆዎች የሚያመሳስላት ነገር የለም።  

ኪም ፖተር ዳኡንትን በትራፊክ መብራት ዳር ባስቆመችበት ጊዜ ምልምል የ ፖሊስ አባላትን እያሰለጠነች ነበር። የዳኡንትን እጅ ልታስር በሞከረችበት ወቅት ወደኋላ በማፈግፈጉ ብቻ መሳርያዋን ልትመዝ ችላለች። እንደ ተከሳሽዋ ንግግር ከሆነ በግዜው ቴዜር የተባለ ጊዚያዊ አቅም ማዳከምያውን እንጂ መሳርያ ለመጠቀም አስባ አልነበረም። ይሁን እንጂ ቴዘርን እና ሽጉጥን በተቃራኒ በኩል ወገብ ጋር አድርጎ ማስቀመጥ የፖሊሶች ደንብ ነው። ይህን አዲሷ የኪም ሰልጣኝ የምታስታውሰው ቢሆንም የ 26 አመቷ ኪም ግን ዘንግታዋለች።

ኪም በስህተህ ሽጉጧን አውጥታ በተደጋጋሚ ‘ቴዘር’ ብላ በመጮህ የሽጉጧን ምላጭ ስባ ዱኣንትን ለሞት ዳርጋዋለች። የኪም በ ዳኡንት ላይ የነበራት ፍራቻ እና ሽጉጧን ይዛ በሽራፊ ሰከንዶች ውስጥ በሰራችው ስህተት እና የተከተለው ፀፀት ከ ቀድሞው የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ኦፊሰር መሀመድ ኑር ጋር የሚመሳሰል ነው።

በ ሀምሌ 15/2017 ነበር ሙሐመድ የጀስቲንን የ 911 የአደጋ ጊዜ ጥሪ የመለሰው። ከቤቷ ጀርባ የሰማችው ድምጽ የፆታዊ ጥቃት ሊሆን ይችላል ብላ በመገመት ነበር ለማመልከት የደወለችው። ሙሐመድም ወደ ቦታው የሄደው ከስራ ባልደረባው ማቲው ሃሪቲ ጋር ነበር። ማቲው ለፍርድ ቤት በሰጠው ቃል ቦታው ላይ በነበረበት ጊዜ ጀስቲን መኪና ስታስነሳ በሰማው ድምጽ ፈርቶ እንደነበር ይናገራል። በዚህ ግዜ ነው ሙሐመድ ባልደረባው ማቲው “ወይኔ ፈጣሪ” ሲል የሰማው። በዚህ መሀከል ነው ጀስቲን እጅዋን ስታነሳ ሙሐመድ ኑር በቅፅበት ቃታውን ለመሳብ የተገደደው። በ ኪም ፖተር የተፈፀውም ቅፅበታዊ እርምጃ ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ነበር።

ልብሷ ላይ ያለው ካሜራ እንደሚያሳየው ኪም ዳኡንት ላይ ከተኮሰች በኋላ “ተኮስኩበት” ብላ በሲቃ ጮሃለች። በተመሳሳይ ሁኔታ መሀመድ “ወደ ወይዘሮ ጀስቲን ቀረብ ብሎ እያጣረች ባለችበት ሰአት ስደርስ ጥፋተኝነት ተሰማኝ። በዛች ቅፅበት ነው ልክ እንዳልነበርኩ ተረዳሁ።” ብሏል።

ዱኣንትን መግደል ልክ እንዳልነበረው ሁሉ ጀስቲንን መግደልም ልክ አልነበረም። የሁለቱ ፖሊስ ኦፊሰሮች ድሪጊት ልክ አለመሆኑን ከተስማማን እጅግ የተራራቀ ውሳኔ ለምን ተሰጣቸው? የካቲት 18/2022 ላይ የሚኒኣፖሊስ ፍ/ቤት ኪም ላይ የ ሁለት አመት የፈረደባት ቢሆንም እስራቱ ለ24 ወራት ይቆያል ማለት አይደለም። ለ 16 ወራት በእስር ከቆየች በኋላ ክትትል እየተደረገላት የምትለቀቅ ይሆናል። 

የዳኡንት እናት ኬቲ ራይት ዳኛው በልጅዋ ገዳይ ላይ ከፍተኛ ቅጣት እንዲጣልባት ዳኛውን ብትጠይቅም በተቃራኒው በተሰጠው ውሳኔ መደናገጧ ግን አልቀረም። ኬቲ ኪምን ይበልጥ ያስጨነቃት ተኩሳ የገደለችው ዱኣንት ሳይሆን ስራዋ እና የወደፊት እጣ ፈንታዋ ነው። ትላለች አስከትላም “የዱኣንትን ህልም ነጥቀሻል።” ስትል የፖሊስ ኦፊሰርዋን ኮንናለች። በዳኛው ውሳኔ የተከፉት የ ራይት እናት “ኪም ፖተር ልጄን በሚያዛ 11 ገላዋለች። ዛሬ ደግሞ የፍትህ ስርአቱ በውሳኔው በድጋሜ ገሎታል።” ብላለች። 

በሌላ በኩል ዳኛው ረጊና ይሀንን ጉዳይ ከ ጆርጅ ፍሎይድ ግድያ ጋር አነጻጽሮታል። “ይህቺ ፖሊስ በጉልበቷ የተጎጂው አንገት ላይ ጉልበቷን በማሳረፍ ለዘጠኝ እና ግማሽ ሰከንዶች ትንፋሽ እስኪያጥረው ድረስ ቆማበት ሳይሆን በስህተት የሰራቸው ወንጀል ነው።” ብሏል።

ዳኛው የኪምን ወንጀል ከጆርጅ ፍሎይድ ገዳይ ጋር ሲያነፃፅሩ የሙሐመድ ቤተሰቦች በተራቸው የኪምን ፍርድ እስር ቤት ውስጥ ካለው ሙሐመድ ጋር እያነጻጸሩት ይሆናል። ሁለቱም ተከሳሾች ግድያውን የፈጸሙት በስህተት ከሆነ የተወሰነባቸው ውሳኔ ግን ይህንን አያሳይም። መሀመድ ለሰራው ስህተት የ 12 አመት እስራት ተፈርዶበታል።

ሙሐመድ ስራ ላይ ሆኖ ተኩሶ በመግደል የመጀመርያው የሚኒሶታ ፖሊስ ሲሆን በሚገርም ሁኔታ ከ አንድ አመት በፊት በ 2016 ኦፊሰር ጄሮኒሞ ያኔዝ ፊላንዶ ካስቲልን ተኩሶ ገድሎታል። ፊላንዶ ከሴት ጓደኛው ጋር  መኪና ሲነዳ ነበር ኦፊሰሩ ያስቆመው። ኦፊሰር ጄሮኒሞ ካስቲል ሽጉጡን እንዳያነሳ ይነግረዋል። ፊላንዶም “አላወጣሁም” ሲል መለሰ። ጄሮኒሞ ደጋግሞ “ ሽጉጥ እንዳታወጣ” ሲል የፊላንዶ ፍቅረኛ “እያወጣ አይደለም” እያለች የነበረ ቢሆንም ጄሮኒሞ ፊላንዶ ላይ ለሰባት ጊዜ ያህል ተኩሶበትላ። ፊላንዶ  ከ20 ደቂቃ በኋላ በሄኔፒን የህክምና ማእከል ሞተ። ጄሮኒሞም በአምስት ቀናት ውስጥ ከሁሉም ክሶች ነጻ ተባለ።

እንደ እድል ሆኖ የመሀመድ ጠበቆች  ለመሀመድ መሟገታቸውን አላቆሙም። አቃቤ ህግ ፒተር ዎልድ “ኑር በሽራፊ ሴኮንዶች ውስጥ እርምጃ በመውሰድ ወይዘሮ ጀስቲንን በጥይት ተኩሶ የገደላት በነበረበት ፍርሃቻ ምክያት እንደሆነ ጥያቄ የለውም።” ብሏል። ሌላው ተከላካይ ጠበቃ ቶማስ ፕሉንኬት እንደተናገረው “ፍርድ ቤቱ መሐመድን ለ150 ወራት እስር ቤት እንዲቆይ በመወሰኑ ቅር ተሰኝተናል። መደረግ ያለባቸው ሂደቶች ላይ ምልከታ እናደርጋለን። ለመሀመድ ኑር መቆማችንን እንቀጥላለን።” ብሏል። 

በመሀመድ ጠበቆች ያላሰለሰ ጥረት እና መሀመድን ለመደገፍ ለፍርድ ቤት በተላኩ በርካታ ደብዳቤዎች ምክንያት ጥቅምት 2021 የሀገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የመሀመድን የ3ተኛ ደረጃ ግድያ ጥፋተኛነት ሽሮታል። ከዚያም ከአምስት ዓመት በታች በእስር እንዲቆይ ተፈርዶበታል። ምን አልባትም የእስር ጊዜውን የሚጨርስ ከሆነ በዚህ ክረምት ሊፈታ ይችላል። በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የመሀመድን የቅጣት ውሳኔ ቢቀንስም ቀድሞ ተፈርዶበት የነበረው  የ12 ዓመት ተኩል ቅጣት  በፍትህ አሰጣጡ ላይ ጥያቄን ያስነሳል ምክንያቱም የኪም የሁለት አመት የእስር ቅጣት ውሳኔ በኩልነትን ላይ የተመሰረተ ፍትህን ከመስጠት ጋር ሊጣረስ ይችላል።

ይህ የፍትህ አሰጣጥ ልዩነት የመጣው በፖሊሶቹ የቀለም ልዩነት ሳይሆን  የተፈረደባቸው በተፈፀሙት ወንጀል ብቻ ነው ብሎ ለመገመት አስቸጋሪ ነው። ምን አልባትም የቀለም ልዩነት በራሱ ብዙውን ጊዜ ፍርድ እንዴት እንደሚሰጥ ይወስናል። እንዲሁም ተጎጂዎቹ በነሱ ላይ በተፈፀመው ወንጀል ብቻ እንጂ በ ቀለማቸው ልዩነት አይደለም የተፈረደላቸው ብሎ ለማለትም አስቸጋሪ ያደርገዋል።

እንደ እድል ሆኖ የመሀመድ ጠበቆች  ለመሀመድ መሟገታቸውን አላቆሙም። አቃቤ ህግ ፒተር ዎልድ “ኑር በሽራፊ ሴኮንዶች ውስጥ እርምጃ በመውሰድ ወይዘሮ ጀስቲንን በጥይት ተኩሶ የገደላት በነበረበት ፍርቻ ምክያት እንደሆነ ጥያቄ የለውም።” ብሏል። ሌላው ተከላካይ ጠበቃ ቶማስ ፕሉንኬት እንደተናገረው “ፍርድ ቤቱ መሐመድን ለ150 ወራት እስር ቤት እንዲቆይ በመወሰኑ ቅር ተሰኝተናል። መደረግ ያለባቸው ሂደቶች ላይ ምልከታ እናደርጋለን። ለመሀመድ ኑር መቆማችንን እንቀጥላለን።” ብሏል። 

በሙሀመድ ጠበቆች ያላሰለሰ ጥረት እና መሀመድን ለመደገፍ ለፍርድ ቤት በተላኩ በርካታ ደብዳቤዎች ምክንያት ጥቅምት 2021 የሀገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የመሀመድን የ3ተኛ ደረጃ ግድያ ጥፋተኛነት ሽሮታል። ከዚያም ከአምስት ዓመት በታች በእስር እንዲቆይ ተፈርዶበታል። ምን አልባትም የእስር ጊዜውን የሚጨርስ ከሆነ በዚህ ክረምት ሊፈታ ይችላል። በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የመሀመድን የቅጣት ውሳኔ ቢቀንስም በተመሳሳይ ክስ ኪም የሁለት አመት እስር ተፈርዶባት በተቃራኒው እርሱ ላይ የ 12 አመት ተኩል ውሳኔ መስጠቱ የፍርድ ቤቱን ፍትሀዊነት ጥያቄ ውስጥ ይከታል።

ይህ የፍትህ አሰጣጥ ልዩነት የመጣው በፖሊሶቹ የቀለም ልዩነት ሳይሆን የተፈረደባቸው በፈፀሙት ወንጀል ብቻ ነው ብሎ ለመገመት አስቸጋሪ ነው። በተደጋጋሚ እንደታየው የቀለም ልዩነት የፍርድ አሰጣጡን ይወስናል። ይህም ተጎጂዎቹ በፈፀሙት ወንጀል ብቻ ነው ፍርድ የተሰጣቸው ለማለት አዳጋች ያደርገዋል።

Related Posts

Ethiopian
ብሔራዊ

ከአትላንታ ወደ ኢትዮጵያ የሚደረግ አዲስ የቀጥታ በረራ ተጀመረ!

January 26, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate
ብሔራዊ

ዘይነብ መሀመድ በሚኒሶታ ሴኔት ቃለ-መሀላ ፈፀመች

January 6, 2023
Ilhan Omar’s Receives Death Threat – Frank Pezzuto Sentenced to 15 Months
ብሔራዊ

ኢልሃን ኦማር ላይ የሞት ዛቻ ያደረገው ፍራንክ ፔዙቶ ለ 15 ወራት ተፈርዶበታል

July 8, 2022
Adhan አዛን
ብሔራዊ

አዛን – የሙስሊሞች የሰላት ጥሩ በሚኒያፖሊስ ህጋዊ ሆነ!

July 8, 2022
Islamophobia
ብሔራዊ

እየጨመረ የመጣው የእስልምና ጥላቻ በዋሺንግተን አዲስ ወንጀል አስከተለ!

July 8, 2022
ሮይስ ኋይት
ብሔራዊ

የቀድሞው የ ኤንቢኤ ተጫዋች ሮይስ ኋይት የኢልሀን ወንበር ለመቀማት ለኮንግረስ እጩ ተወዳዳሪ ሆነ!

July 8, 2022

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

POPULAR POST

No Content Available
Load More

RECENT POST

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

March 8, 2023
Ethiopian

New Direct Flights from Atlanta to Ethiopia

January 25, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

January 6, 2023
Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

December 19, 2022
Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

December 13, 2022
Horn Magazine

The Horn Magazine is a U.S. based, online magazine that serves to provide meaningful articles on a variety of subjects that impact your daily lives.

Contact info@hornmagazine.com

CATEGORIES

English                Amharic                 Somali 
National                ብሔራዊ                    Qaran
World                     ዓለም                      Adduunka
Sports                    ስፖርት                   Ciyaaraha
Finance                  ፋይናንስ                 Maaliyadda
Health                    ጤና                       Caafimaadka
Education              ትምህርት                Waxbarasho
Entertainment      መዝናኛ                   Madadaalo

SUBSCRIBE NEWSLETTER

Loading
  • About
  • Advertise
  • Privacy & Policy
  • Contact

© 2021 Horn Magazine

No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health

© 2021 Horn Magazine