Horn Magazine
Wednesday, May 14, 2025
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
Horn Magazine
No Result
View All Result

Home » ፖሊስ የግለሰብ ቤት ሳያንኳኳ ወደ ውስጥ እንዲገባ የሚፈቅድ ትዕዛዝ የሚሽር አዲስ ህግ በ ኢልሃን ኦማር ረቀቀ!

ፖሊስ የግለሰብ ቤት ሳያንኳኳ ወደ ውስጥ እንዲገባ የሚፈቅድ ትዕዛዝ የሚሽር አዲስ ህግ በ ኢልሃን ኦማር ረቀቀ!

March 28, 2022
in Uncategorized
1 min read
አዲሷ ሱማሌ አሜሪካዊ የኢልሀን ተቀናቃኝ ሹክሪ ፟ Shukri ፖሊስ
ShareSharePin

መጋቢት 2020 አሜሪካውያን በ ጆርጅ ፍሎይድ አሰቃቂ ግድያ ሳይቀጣ እና እልባት ሳይገኝለት እንዳይቀር በትትብብር የቆሙበት ወሳኝ ታሪካዊ ግዜ ነበር። የአንድነቱ ፍሬም በሚኒሶታ ግዛት ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ ነበር። ግዜው ለመጀመርያ ግዜ ነጭ የ ፖሊስ ባልደረባ በስራ ላይ እያለ ተኩሶ ግድያ በመፈፀሙ ለመጀመርያ ጊዜ ለጥፋቱ እርምጃ የተወሰደበት ነበር።

ፍሬያማ ተስፋን ያዘለ የሚመስለው የፍትህ ስርዐቱ ምን አልባትም ያ አሳዛኝ ክስተት በድጋሚ ሊፈጠር እንደማይችል በህዝቡ ልብ ውስጥ አመኔታን ፈጥሮ ሊሆን ይችላል። በተለይም ሚኒያፖሊስ ውስጥ በሚገኘው የጆርጅ ፍሎይድ ምስል በታሪክነት ተስሎ በተቀመጠበት 38ኛው መንገድ ዳር እና ቺካጎ ኤቭ  እንዲሁም በሁሉም ሚኒሶታ አከባቢዎች በድጋሚ በጭራሽ ሊከሰት ይችላል ተብሎ አይታሰብም። ይሁን እንጂ የዚህ አይነት አሳዛኝ ግድያዎች ዳግም መፈጠራቸው አልቀረም። 

ከሀያ ሶስት ወራት በኋላ የካቲት 2 ላይ አሚር ሎክ ከንጋት በፊት የሚኒያፖሊስ ፖሊሶች ሳያንኳኩ ቤቱን ከወረሩት በኋላ ግድያ ተፈጽሞበታል። የ ፖሊስ ቡድኑ የአሚርን መኖርያ ቤት የከበቡት በግድያ ወንጀል ተጠርጣሪ የነበረውን የአሚርን የአጎት ልጅ ለመያዝ ነበር። ታድያ ይህ ክስተት በኢልሃን ኦማር የቀረበውን አዲስ ህግ ለማምጣት መንገድ ከፍቷል። 

ኢልሃን “ፖሊሶች ለባለቤቱ ሳያሳውቁ የግለሰቡን ቤት በመውረር መግባት እስካሁን በሰው እና በንብረት ላይ ከባድ እና አስከፊ ጉዳቶችን አስከትሏል። ሳያንኳኩ ወደ ግለሰብ ቤት መግባት ካለ ምንም ገደብ፣ ህግ እና ደንብ እንዲሁም በሰዎችህ ህይወት ላይ ስለሚያመጣው ተጽዕኖ ቦታ ሳይሰጠው ስራ ላይ መዋሉ ምክንያታዊ አይደለም።” ብላለች።    

በስተመጨረሻም ፖሊሶቹ የካቲት 8 ላይ የአሚርን የአጎት ልጅ አግኝተው አስረውታል። ይሁን እንጂ አሚር ጥፋተኛው በተያዘበት ጠዋት በመኖርያ ቤቱ ውስጥ ተገሎ ተገኝቷል። አሚር ላይ ጥይቱን የሳበው ፖሊስ ደሞዙ ሳይቋረጥበት ለተወሰኑ ጊዜያት ከስራ ውጪ ሆኗል። 

የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ጊዜያዊ አመራር የሆነችው ኤሚሊያ ሁፍማን “ፖሊሱ ወደ አሚር መኖርያ ቤት ከመግባቱ በፊት ጮክ ብሎ ‘የፖሊስ የፍተሻ ትዕዛዝ ነን!’ ሲል አሳውቋል።” ብላለች። ነገር ግን በፖሊሱ ልብስ ላይ ያለው ካሜራ ይህንን የሚቃረን ሆኖ ተገኝቷል። ይልቁንም ካሜራው የሚያሳየው ፖሊሶቹ ወደ መኖርያ ቤቱ እየተቻኮሉ በመሄድ ለራሳቸው እያሳወቁ እንደነበር ነው። ይህም ምን አልባት አሚርን አስደንግጦት ህጋዊ የሆነውን ሽጉጡን እንዲይዝ አድርጎት ይሆናል። 

በተጨማሪም ኤሜሊያ የአሚር ሽጉጥ ፖሊሶቹ ላይ ያነጣጠረ ነበር ብላለች። ነገር ግኝ በድጋሚ ካሜራው እንደሚያሳየው ከሆነ የሽጉጡ ኢላማ መሬት ላይ ነበር። አሚር በተገደለበት ማግስት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አሜሊያ አሚር ቀደም ብሎ በሌላ የግድያ ወንጀል ተጠርጣሪ የነበረ መሆኑን ገልፃለች። ይሁን እንጂ የፖሊስ ዘገባው በግልፅ እንደሚያሳየው ፖሊሶቹ የአሚርን ማንነት የለዩት ግድያው ከተፈጸመ ከአንድ ሰአት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ነበር። 

ለዚህ አሰቃቂ ግድያ ምላሽ በመስጠት በመጋቢት መጀመርያ ላይ ኢልሃን ኦማር እነዚህን የመሳሰሉ ግድያዎች እንዳይፈጠሩ ሊከላከል እንደሚችል የሚታሰብ ‘የአሚር ሎኬ ሳያሳውቁ ወረራ የማድረግ ህግን መቋጨት!’ የሚል አዲስ ህግ አርቅቃለች። ህጉ በፍጥነት ወረራ ማድረግን ጨምሮ ሳያንኳኩ ቤትን ወይም ንብረትን እንዲወሩና እንዲፈትሹ የሚፈቅደው ህግ በማታ ስራ ላይ እንዳይውል ሊከለክል ይችላል። ከሁለት አመት በፊት ብሬኦና ቴይለር በተመሳሳይ ምክንያት ህይወቷን ስታጣ ሳያንኳኩ ቤትን የመውረር ህግ እንዲሰረዝ የሚፈልጉ አያሌ ድምጾች ተስተጋብተው ነበር። ኢልሃንም ይህንን ድምጽ ህግ ሆኖ ወደ ተግባር እንዲቀየር አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። 

ብሬኦና ህይወቷ ካለፈ ከአጭር ጊዜ በኋላ ኮንግረስማን ራንድ ፓኡል ፍትህ ለብሬኦና የሚል ህግ አርቅቆ ነበር። በ ሉዊዝቬል ኬንታኪ በዚህ ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር አስገራሚ በሆነ ደረጃ ቀንሷል። የኬንታኪ ማእከላዊ የምርመራ መረጃ እንደሚጠቁመው በ ሉዊዝቬል ያሉ ፖሊሶች በ አስራ አራት ወራት ውስጥ አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ ለአራት ጊዜ ብቻ ሳያንኳኩ ወረራ አድርገዋል።

የጆርጅ እና ብሬኦናን ግድያን ተከትሎ በህዳር 2020 የሚኒያፖሊስ የ ፖሊስ ክፍል ሳያንኳኩ ወረራ ማድረግ ላይ የተወሰነ እገዳ የሚጥሉ ማሻሻያዎችን አውጥቷል። በግዜው የ ፖሊስ ክፍሉ በአመት 139 ሳያንኳኩ ተጠርጣሪን የመውረር ስራዎች እንደተሰሩ ገልጿል። ማሻሻያው ስራ ላይ ከዋለ በኋላ በዘጠኝ ወራት 90 የሚሆኑ ሳያንኳኩ የግለሰብ ቤት ውስጥ የመግባት ድርጊቶች ተፈጽመዋል። ከማሻሻያው በኋላ በታየው ውጤትም በርካታ የሚኒሶታ ማህበረሰቦች ደስተኛ አይደሉም። ታዲያ ኢልሃንም ይሄንን ለመቀየር ቆርጣ ተነስታለች። 

ኢልሃን “ሳያንኳኩ ወረራ ማድረግ ከ ዘር እንዲሁም ጥቁር ቀለም ካላቸው ሰዎች ጋር የተቆራኘ ልዩነት ላይ የተመሰረተ ጥልቅ ታሪክ አለው። ይህም ሌላኛው ፖሊሶች የሰዎችን ክብር ለመሸርሸር ተግባር ላይ እያዋሉት ያለ ዘዴ ነው።” ብላለች። 

ከ አሚር ህልፈት በኋላ የሚኒያፖሊስ ሀላፊ ጃኮብ ፍሬይ በሁለት የሀገሪቱ ሊቆች ሳያንኳኩ ወረራ ማድረግ ላይ ቀጣይ ምርመራዎች እስኪደረግ ድረስ ሳያንኳኩ ወረራ ማድረግን የሚያግድ ትእዛዝ አውጥተዋል። እስካሁን ድረስ የ አሚር ጉዳይ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል። 

Related Posts

four Islamic centers were attacked in the past six months in western Washington
Uncategorized

በሃይማኖታዊ ድርጅቶች ላይ የሚደርሰውን በርካታ ጥቃቶችን ተከትሎ የአሜሪካ ሙስሊም ወጣቶች ማእከል የአንድነት ቀን አካሄደ!

March 30, 2022

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

POPULAR POST

No Content Available
Load More

RECENT POST

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

March 8, 2023
Ethiopian

New Direct Flights from Atlanta to Ethiopia

January 25, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

January 6, 2023
Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

December 19, 2022
Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

December 13, 2022
Horn Magazine

The Horn Magazine is a U.S. based, online magazine that serves to provide meaningful articles on a variety of subjects that impact your daily lives.

Contact info@hornmagazine.com

CATEGORIES

English                Amharic                 Somali 
National                ብሔራዊ                    Qaran
World                     ዓለም                      Adduunka
Sports                    ስፖርት                   Ciyaaraha
Finance                  ፋይናንስ                 Maaliyadda
Health                    ጤና                       Caafimaadka
Education              ትምህርት                Waxbarasho
Entertainment      መዝናኛ                   Madadaalo

SUBSCRIBE NEWSLETTER

Loading
  • About
  • Advertise
  • Privacy & Policy
  • Contact

© 2021 Horn Magazine

No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health

© 2021 Horn Magazine