Horn Magazine
Wednesday, May 14, 2025
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
Horn Magazine
No Result
View All Result

Home » የዩክሬን ጦርነት የአለም ምግብ አቅርቦት ላይ ስጋት ጣለ!

የዩክሬን ጦርነት የአለም ምግብ አቅርቦት ላይ ስጋት ጣለ!

March 21, 2022
in ዓለም
1 min read
Russia Ukraine War threatens world food supply
ShareSharePin

የሩስያ እና ዩክሬን ግጭት በሚሊዮን በሚቆጠሩ ዩክሬናዊያን ተፈናቃዮች ላይ ጥፋትን ከማስከተሉ ባሻገር ግጭቱ አለም ላይ በቢሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች ላይ አሉታዊ ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖው ተስተውሏል። አፍሪካም ከሌሎች አካባቢዎች በከፋ ሁኔታ ተፅዕኖዎን በምግብ እጥረት እየተጋራች ትገኛለች።

ሩስያ እና ዩክሬን የአለምን አንድ ሶስተኛ የግብርና አቅርቦት ስለሚሸፍኑ የዓለም የምግብ አቅርቦት በከፍተኛ ደረጃ በሩሲያ እና ዩክሬን ለም የእርሻ መሬቶች ላይ የተመሰረተ ነው። ለም የእርሻ መሬቱ እንደ ስንዴ እና በቆሎ ያሉ እህሎችን እንዲሁም የሱፍ አበባ ዘይት፣ ማዳበሪያዎች እና የኃይል ምንጮችን ያመርታል። ከሌሎች አካባቢዎች በተለየ አፍሪካም መሰረታዊ የምግብ ፍላጎቶችን ለማሟላት በእነዚህ ሁለት ምንጮች ላይ ጥገኛ ናት።

ጦርነቱ ገበሬዎች እንዲሰደዱ ከማስገደዱ በተጨማሪ እንደ ቼርኒሂቭ፣ ፖልታቫ፣ ካርኪቭ፣ ሱሚ እና ዢቶሚር የመሳሰሉ የዩክሬን ግብርና የተመሰረተባቸው ቁልፍ ከተሞች እንዲወድሙ ምክንያት ሆኗል። በሀገሪቱ የምግብ እጥረት እንዳይከሰት ዩክሬን የግብርና ምርቶቿን ወደ ውጭ ከመላክ ተቆጥባለች። ብዙም ሳይቆይ ሩሲያም የግብርና ምርቶችዋን ከሀገር ውስጥ ገበያ ውጪ ወደ ውጪ እንዳይላክ እገዳ ጥላለች።

የዩክሬን የግብርና ሚኒስትር ሮማን ሌሽቼንኮ “በዩክሬን ያለውን ሰብዓዊ ቀውስ ለመከላከል የግብርና ምርትን ወደ ውጭ መላክ መታገድ ይኖርበታል!” ብለዋል። ውሳኔው ገበያውን ለማረጋጋት እና ወሳኝ በሆኑ የምግብ ምርቶች ላይ የህዝቡን ፍላጎት ለማሟላት መሆኑንም ገልፀዋል። እገዳው ማሽላ፣ ቡክኄት፣ ስኳር፣ ከብቶች እና የከብት ተረፈ ምርቶች ወደ ውጭ መላክ ማቆምን ያካትታል።

ጦርነቱ በተጀመረ በሁለት ሳምንት ውስጥ ብቻ የ ምግብ ዋጋ 55 በመቶ ጨምሯል። የ ዩክሬን መንግስት የ ህዝቦቹን የምግብ ዋስትና ለመጠበቅ ስንዴ፣ አጃ እና ሌሎች ዋና ዋና ምርቶችን ወደ ውጭ እንዳይላኩ አግዷል። ይህም ከ ዩክሬን ድንበር ውጭ ያሉ ሀገራት እነዚህን መሰረታዊ ፍላጎቶች ከማግኘት ያግዳቸዋል።
በተባበሩት መንግስታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የንግድ እና ገበያ ክፍል ኢኮኖሚስት የሆኑት ኤሪክ ኮሊየር “ዩክሬን በብዛት በቆሎ የምትልክላቸው ሀገራት ቻይና እና በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ያሉ ሀገራት ናቸው።” ብለዋል ። አክለውም “እነዚህ ሀገሮች ከዩክሬን ውጪ ካሉ ሌሎች ሀገሮች የምግብ አቅርቦቶችን የማስገባት አቅም አላቸው። ይሁን እንጂ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከዩክሬን ውጭ እህል የማስመጣት አቅም የሌላቸው ሲሆን ዋነኛው የምግብ ምንጫቸውም ከውጪ በሚያስገቡት በቆሎ ላይ የተመሰረተ ነው።” ብላለች።

ባሳለፍነው 2020 አፍሪካ 4 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ የግብርና ምርቶችን ከሩስያ አስገብታለች። ከዚህ ውስጥ 90 በመቶ የሚሆነው ምርት ስንዴ ሲሆን ከዚህ ላይ 50 በመቶ የሚሆነው ግብጽ የምታስገባው ነው። ከግብጽ ውጪ ሱዳን እና ናይጄሪያ ስንዴን በዋነኝነት ያስገባሉ። ዩክሬን በ 2020 2.9 ቢሊዮን ዶላር የሚያስገኝ የግብርና ምርት ለአለም ሀገራት ስትልክ ስንዴ እና በቆሎ ትልቁን ድርሻ ይይዛሉ።

ላለፉት ጥቂት አመታት በኢኮኖሚ ሲችገሩ ለቆዩ ሀገራት የምግብ ዋጋ መናር ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል። የደቡብ አፍሪካ የግብርና ቢዝነስ ቻምበር ዋና ኢኮኖሚስት ዋንዲሌ ሺልቦ እንዳሉት “የምግብ ዋጋ እጅጉን ጭማሪ አሳይቷል። ጦርነቱ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አፍሪካውያን ለርሀብ ሊዳረጉ ይችላሉ። በድርቅ በተጎዱ አካባቢዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች በረሃብ ሊጠቁ እንደሚችሉ ገምተናል። በሁለቱ ሀገራት መሀከል ያለው ግጭት ደ’ሞ ረሃቡን ያባብሰዋል።” ብለዋል።

በዛ ያሉ ተንታኞች የስንዴ እና የግብርና ምርቶች እጥረት እስከ 2022 መጨረሻ እንደማይታይ ምሁራዊ ትንበያቸውን ቢያስቀምጡም ግብፅ 50% የሚጠጋውን ስንዴ ከውጭ የምታስገባ በመሆኑ የምግብ ዋጋ ንረት ከወዲሁ በ50 በመቶ ጨምሯል።

ጦርነቱ በአፍሪካ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ቢኖረውም አንዳንድ የኢስያ ሀገራትም ስጋት ላይ ወድቀዋል። እንደ ባንግላዲሽ፣ ሶሪያ፣ ኢራቅ፣ ኢራን፣ የመን፣ ቱርክ እና ፓኪስታን ያሉ ሀገራት ከሩሲያ እና ዩክሬን በሚመጣ ስንዴ ላይ ጥገኛ ናቸው።

ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ሊባኖስ ከሩሲያ እና ከዩክሬን ሦስት አራተኛ የሚሆነውን የሀገሯን የስንዴ ፍጆታ ታስገባ ነበር። ነገር ግን ሁለቱም ሀገራት የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ መላክ ስላቋረጡ የምግብ ዋጋ እየጨመረ መጥቷል። በተጨማሪም በየመን ያለው ግጭትና የዋጋ ንረት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለረሀብ ዳርጓቸዋል። የመን 40% የሚጠጋ ስንዴ ከሩሲያ እና ከዩክሬን ታስገባለች። ታድያ ይህንን መሰረታዊ የምግብ ምንጭ ማጣት የሚያስከትለው መዘዝ ወደ አስከፊ የሰብአዊ ቀውስ እንደሚመራ የሚጠብቅ ነው።

የሩስያ እና ዩክሬን ቀውስ በኢኮኖሚ እና በመሠረታዊ የመተዳደሪያ መስፈርቶች ላይ ዓለም አቀፋዊ ተጽእኖ እያሳደረ መምጣቱ ግልጽ ነው። ሆኖም ጦርነቱ በዓለም ዙሪያ ሊያስከትለው የሚችለውን ችግሮች ከመገመት በዘለለ እስካሁን ምንም አይነት የመፍትሄ ሀሳቦች አልተገኙም። ምን አልባትም ጦርነቱ የሚያመታጣው መዘዝ አለም ከ ሁለተኛው የአለም ጦርነት በኋላ ያላየችው ነገር ሊሆን ይችላል።

Related Posts

Dr. Tedros
ዓለም

አለም ከዩክሬን ጋር እያዘነ ባለበት ጊዜ የአለም የጤና ድርጅት ዋና ሃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በ አፍሪካ ስላለው ግጭት መከሩ

April 25, 2022
rubel ሩብል
ዓለም

የራሺያ ሩብል የተለያዩ ማዕቀቦች ቢጣሉበትም በአጭር ግዜ አንሰራራ!

April 19, 2022
Israel Attempts to Ban Ethiopians for Easter እስራኤል
ዓለም

እስራኤል የኢትዮጲያውያን ጉዞ እግድ አነሳች!

April 15, 2022
Ethiopian Government Declares Humanitarian Truce with Tigray - የኢትዮጵያ
ዓለም

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት የሰብአዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆን ከ ህወሀት ጋር የተኩስ አቁም አወጀ!

April 4, 2022
Worldwide Mercenaries Seeking to Help Ukraine ዜሌኒስኪ
ዓለም

አለም አቀፍ ተከፋይ ጦረኞች ዩክሬንን ለማገዝ ፍቃደኝነታቸውን አሳዩ!

March 24, 2022
African Nations Divided on the Russia-Ukraine Crisis
ዓለም

አፍሪካውያን በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ላይ የተለያየ አቋም አሳዩ!

March 23, 2022

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

POPULAR POST

No Content Available
Load More

RECENT POST

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

March 8, 2023
Ethiopian

New Direct Flights from Atlanta to Ethiopia

January 25, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

January 6, 2023
Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

December 19, 2022
Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

December 13, 2022
Horn Magazine

The Horn Magazine is a U.S. based, online magazine that serves to provide meaningful articles on a variety of subjects that impact your daily lives.

Contact info@hornmagazine.com

CATEGORIES

English                Amharic                 Somali 
National                ብሔራዊ                    Qaran
World                     ዓለም                      Adduunka
Sports                    ስፖርት                   Ciyaaraha
Finance                  ፋይናንስ                 Maaliyadda
Health                    ጤና                       Caafimaadka
Education              ትምህርት                Waxbarasho
Entertainment      መዝናኛ                   Madadaalo

SUBSCRIBE NEWSLETTER

Loading
  • About
  • Advertise
  • Privacy & Policy
  • Contact

© 2021 Horn Magazine

No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health

© 2021 Horn Magazine