Horn Magazine
Thursday, May 15, 2025
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
Horn Magazine
No Result
View All Result

Home » የ ዋትስአፕ ተጠቃሚዎች የግል መረጃ ተጋላጭነት

የ ዋትስአፕ ተጠቃሚዎች የግል መረጃ ተጋላጭነት

ፌስቡክ የተጠቃሚዎችን መረጃ ከዋትስአፕ መውሰድ እንደሚጀምር አሳወቀ

July 8, 2022
in ብሔራዊ
1 min read
ዋትስአፕ
ShareSharePin

የስልክ ጥሪዎች፣ የመለክት ልውውጦች እንዲሁም የቪዲዎ ጥሪዎች ሁሉም ነጻ ናቸው። በ ዋትስአፕ እኚህን ለማከናወን ምንም አይነት ገንዘብ ማውጣት አይጠበቅብዎትም። ታድያ ምንድነው ሚስጥሩ? አብዛኞቹ ሰዎች የዋትስአፕን መተግበርያ ወደ ስልካቸው ሲያወርዱ የሚከፍሉት ዋጋ ምን አልባትም ከተወሰኑ ገንዘቦች በላይ እንደሆነ አይገነዘቡም። በ 2014 ዋትስአፕን የግሉ ማድረግ የቻለው ፌስቡክ እየፈለገ ያለው የተጠቃሚዎችን የግል መረጃ እንደክፍያ ሆኖ እንደሆነስ?

ቀደም ብሎ የካቲት 8 ይጀምር የነበረውን ዋትስአፕን መጠቀም እስከፈለጉ ድረስ በዋትስአፕ አዲስ ግላዊነት ፖሊሲ እንዲስማሙ እንደሚገደዱ ያወቁ የዋትስአፕ ተጠቃሚዎች ሁከት በማስነሳታቸው ፌስቡክ በድጋሚ እንዲጀምር የታሰበበትን ቀን እንዲመለከት አድርጎታል። በመሆኑም ፖሊሲው የሚጀምርበት ቅን ወደ ግንቦት እንዲተላለፍ ተደርጓል።  

ፌስቡክ ዋትስአፕን በ  $16 ቢሊየን የገዛው ሲሆን፤  $4 ቢሊየን በጥሬ ገንዘብ እንዲሁም  $12 ቢሊየን ደግሞ በ ፌስቡክ አጋርነት የሚቆይ ነው። በተጨማሪም  $5.3 ቢሊየን ለዋትስአፕ ሰራተኞች እንደ ካሳ የተሰጠ ነው። በአጠቃላይ ፌስቡክ $21.8 ቢሊየን ወጪ አድርጓል። ይህም የዋትስአፕን ዋጋ እና  የሚጠቀሙበትን ሰዎች ብዛት ያሳያል። የፌስቡክ ዋና ስራ አስኪያጅ ማርክ ዙከርበርግም ይህን አጠራጣሪ ውሳኔ ከአስተዋዋቂዎች የሚመጣ ተጨማሪ ገንዘብ ወደ ኪሱ ለማስገባት ሲል ለመወሰን ፍላጎት እንዳደረበት የማይካድ እውነት ነው ።

ዋትስአፕ ተጠቃሚዎች ማስታወቂያዎች ዋትስአፕ ላይ ስለማይመጣላቸው ማስታወቂያ ሰሪዎች የሚፈልጉትን መረጃ ማግኘት አይችሉም። ይሁን እንጂ አሁን ፌስቡክ ዋትስአፕን የግሉ በማድረጉ የተጠቃሚዎችን መረጃ እንዲጠቀም ያስችለዋል። የአሳሽ መረጃ ፣ የሞባይል አውታመረብ፣ የሞባይል ኦፕሬተር እንዲሁም የ አይፒ አድራሻ አንደ ምሳሌነት የሚጠቀሱ ፌስቡክ ከዋትስአፕ የሚወስዳቸው የግለሰቡ መረጃዎች ናቸው።  እነዚህንም መረጃዎች  ከፌስቡክ ስለ ተጠቃሚዎች እንደ እቃ ግዢ ልምድ  ካሉ መረጃዎች ጋር በማጣመር ለከፋይ አስተዋዋቂዎች መሸጥን ነው ኢላማው  ያደረገው።

እውነት ፌስቡክ የህን ያህል እርቀት ይጓዛል ? አስቲ የማርክ ዙከርበርግን የተወሰኑ የቀድሞው ታሪኮች እንመልከት። ከፌስቡክ በፊት በ 2003 ዙከርበርግ “ፌስማሽ” የተሰኘ መተግበርያ ፈጠረ። የ ሀርቫርድ ክሪምሰን የተባለ ጋዜጣም የ ታዋቂው “አም አይ ሆት ኦር ኖት” የተባለ ድህረ ገጽ ስሪት ሲል ገልፆታል። በመሆኑም ዙከርበርግ የ ሀርቫርድ አመራር ቦርድ ጋር በመቅረብ የሰዎችን የግል መረጃ በመጠቀም፣ ደህንነታቸውን እንዲሁም የቅጂ መብትን በመጣስ ተከሷል።

ከአመት በኋላ ፌስቡክን ከአብሮ መስራቾቹ ክሪስ ሂውዝ፣ ደስቲን ማስካቬስት እና ኤድዋርዶ ሳቨረን ጋር በመሆን ፈጥሯል። ፌስቡክን ከጀመረ በኋላ ፌስቡክ ለመጠቀም የሚያስገቡትን መረጃ ተጠቅሞ  የሁለት ክሪምሰን ጋዜጠኞችን የኢሜይል መለያ ጠልፏል።

21 አመት ሳይሞላው የሰራቸው ስህተቶች ምን አልባትም ሊታለፍ ይችል ይሆናል ነገር ግን ዙከርበርግ ከ 15 አመት በኋላ በ2019 በድጋሚ ወደ ፌደራል ንግድ ኮሚሽን በመጠራት ክስ ቀርቦበታል። ፌስቡክ የፌደራል ንግድ ኮሚሽንን የ2012 ትእዛዝ በመተላለፍ ስለተጠቃሚዎች የግል መረጃና ደህንነት በመዋሸት በተጨማሪም በምን ያህል ደረጃ የሰዎችን የግል መረጃ እንደሚጠቀም የተሳሳተ መረጃ በመስጠት  በታሪክ ትልቅ የተባለውን የ$5ቢሊየን የገንዘብ ቅጣት ተቆጥቷል።

የ5ቢሊየን ዶላር ቅጣት በሰዎች የግል መረጃዎች ጣልቃ ገብነትን ለማስወገድ በቂ ይሆናል? ለዙከርበርግና አብረውት ላሉት ይሄ በቂ አይሆንም። ለዚህም ይመስላል በዙከርበርግ እርምጃ የተደመሙ ሰዎች የዋትስአፕ ተቀናቃኝ ወደሆኑ መተግበርያዎች እያመሩ የሚገኙት። ዋትስአፕ በ ዩናይትድ እስቴት እና በ ዩናይትድ ኪንግደም በከፍተኛ ሁኔታ አሽቆልቁሏል:: በዚሁ አመት ጥር መጀመርያ ላይ ዋትስአፕ በትልቁ ከሚወርዱ መተግበርያዎች ውስጥ አንዱ በመሆን ስምንተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ ጥር አጋማሽ ላይ ወደ 23ተኛ ደረጃ ዝቅ ብሏል፡፡ ይህም ለዋትስአፕ “ዋትስአፕ ግላዊነትን ያከብራል እንዲሁም ይጠብቃል፡፡” ሲል ለማወጁ ምክያት ይሆናል፡፡ ሳይዘገይ ግን አልቀረም። 

የቴሌግራም መስራች ፓኡል ዱሮፍ እንደተናገረው “ጥር ላይ በመጀመርያው ሳምንት ቴሌግራም ከ500 ሚሊዮን በላይ ወርሃዊ ተጠቃሚዎችን አግኝቷል።” በማስከተልም “ከዛ በኋላም የተጠቃሚው ቁጥር መጨመሩን ቀጠለ እናም በመጨረሻዎቹ 72 ሰአታት ብቻ 25ሚሊዮን ሰዎች ቴሌግራምን ተቀላቅለዋል።” በ2020 በቀን ከነበረው አማካይ 1.5 ሚሊዮን አዲስ ተጠቃሚዎች ጋር ሲነፃፀር እጅግ የላቀ ለውጥ መሆኑን ገልጿል። “ከዚህ ቀደም ለሰባት አመታት ያህል የቴሌግራም መተግበርያን የሚያወርዱ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ቢመጣም የዚህ ግዜው ግን የተለየ ነው።” ሲል አክሏል።

በተገላቢጦሽ ደ’ሞ በጥር መጀመርያ ከ1,000 በዋናነት ከሚወርዱ መተግበርያዎች ውስጥ እንኳን ያልነበረ ‘ሲግናል’ የተባለ መተግበርያ ወደ አንደኛ ደረጃ መጥቷል፡፡ በተጨማሪም ዋትስአፕ ላይ የተፈጠረውነን ሁካታ ተከትሎ ቴሌግራም የአንዳንድ ሀገራትን ፕሬዝዳንት ቀልብ መሳቡ አልቀረም።የብራዚሉ ፕሬዝዳንት ጃይር ቦልሶናሮ እንዲሁም የቱርኩ ፕሬዝዳንት ታዪብ ኤርዶጋን ቴሌግራምን ተቀላቅለዋል። የበርካቶቹን ዋትስአፕን እየተዉ ወደ ተቀናቃኝ መተግበርያዎች ማምራት “በሰው ልጅ ታሪክ ትልቁ የዲጂታል ስደት ምስክሮች ነን።” ሲል ዱሮፎ አጠቃሏል።

ቁጥሮች እንደሚያሳዩት ምን አልባትም ተጠቃሚዎች ዋትስአፕ የነሱን የግል መረጃ እንደሚጠብቅና እንደሚያከብር ለማመን በመቸገራቸው ዋትስአፕን ለመተው ተገደዋል። የዋትሰአፕ ተወዳዳሪ መተግበርያዎች በምጥቀት ባለሉበት ሰአት ዋትስአፕ ከዙከርበርግ እንዲሁም ከባልደረባዎቹ ጋር በመሆን እንዴት ከገባበተት አዝዕቅት መውጣት እንዳለበትና እንዴት የሰዎችን እምነት በድጋሚ ማግኘት እንዳለበት ማወቅ ይኖርበታል።

Related Posts

Ethiopian
ብሔራዊ

ከአትላንታ ወደ ኢትዮጵያ የሚደረግ አዲስ የቀጥታ በረራ ተጀመረ!

January 26, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate
ብሔራዊ

ዘይነብ መሀመድ በሚኒሶታ ሴኔት ቃለ-መሀላ ፈፀመች

January 6, 2023
Ilhan Omar’s Receives Death Threat – Frank Pezzuto Sentenced to 15 Months
ብሔራዊ

ኢልሃን ኦማር ላይ የሞት ዛቻ ያደረገው ፍራንክ ፔዙቶ ለ 15 ወራት ተፈርዶበታል

July 8, 2022
Adhan አዛን
ብሔራዊ

አዛን – የሙስሊሞች የሰላት ጥሩ በሚኒያፖሊስ ህጋዊ ሆነ!

July 8, 2022
Islamophobia
ብሔራዊ

እየጨመረ የመጣው የእስልምና ጥላቻ በዋሺንግተን አዲስ ወንጀል አስከተለ!

July 8, 2022
ሮይስ ኋይት
ብሔራዊ

የቀድሞው የ ኤንቢኤ ተጫዋች ሮይስ ኋይት የኢልሀን ወንበር ለመቀማት ለኮንግረስ እጩ ተወዳዳሪ ሆነ!

July 8, 2022

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

POPULAR POST

No Content Available
Load More

RECENT POST

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

March 8, 2023
Ethiopian

New Direct Flights from Atlanta to Ethiopia

January 25, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

January 6, 2023
Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

December 19, 2022
Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

December 13, 2022
Horn Magazine

The Horn Magazine is a U.S. based, online magazine that serves to provide meaningful articles on a variety of subjects that impact your daily lives.

Contact info@hornmagazine.com

CATEGORIES

English                Amharic                 Somali 
National                ብሔራዊ                    Qaran
World                     ዓለም                      Adduunka
Sports                    ስፖርት                   Ciyaaraha
Finance                  ፋይናንስ                 Maaliyadda
Health                    ጤና                       Caafimaadka
Education              ትምህርት                Waxbarasho
Entertainment      መዝናኛ                   Madadaalo

SUBSCRIBE NEWSLETTER

Loading
  • About
  • Advertise
  • Privacy & Policy
  • Contact

© 2021 Horn Magazine

No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health

© 2021 Horn Magazine