መቋጫ ያጣው የኢትዮጲያ የእርስ በእርስ ጦርነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት ከመንጠቁ ባሻገር በርካቶችን ለስደትና ለአካል ጉዳት ዳርጓል። ለሁለት ዓመታት ያህል የዘለቀውን የሀገሪቱን አለመረጋጋት ለማስቆም የኢትዮጵያ መንግሥት ከሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ጋር የሰብአዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆን አፋጣኝ የተኩስ አቁም ውሳኔን አውጇል።
የተባበሩት መንግስታት ባወጣው ዘገባ ከህዳር 2020 ጀምሮ ከ5.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የትግራይ ህዝቦች ከውጪው አለም ታግደው ቆይተዋል። እገዳው ከውጪው አለም ጋር የሚደረግ ማነኛውም ግኑኝነት እና ወደሃገሪቱ የሚገባ የሰብአዊ እርዳታንም ይጨምራል።
የፌደራል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት የኢትዮጵያ መንግስት ወደ ትግራይ ክልል የሚደርሰውን የአስቸኳይ ጊዜ ሰብአዊ ርዳታ ነጻ እና ቀላል ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እንደሚያደርግ በመግለጫው አስታውቋል። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ኤጀንሲው በትግራይ ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና በአጎራባች ክልሎች ከያዙት አካባቢዎች እንዲወጡ ጥሪውን አቅርቧል።
ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ በሀገሪቱ ሰላም ለመፍጠር ብዙ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም ተኩስ ለማቆም የተደረጉ ጥረቶች ፍሬ ሲያፈሩ አልታዩም። ነገር ግን አሁን የፌደራል መንግስት በዚህ የእርቅ ስምምነት ላይ የትግራይ ፍላጎት እንዲኖር የተቻለውን አድርጓል ። ህወሓት በትዊተር ገፁ ላይ በሰጠው ምላሽ ይህንን ጸብ ለማቆም ያለውን ዝግጁነት አሳይቷል። ይህም የፌደራል መንግስት ጦርነቱ እንዳቆመ ያረጋግጣል።
የፌደራል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት በሚዲያ መግለጫ ላይ እንደተናገረው “የኢትዮጵያ መንግስት ይህ የእርቅ ስምምነት ያለውን የሰብአዊ ድጋፍ ሁኔታ በእጅጉ እንደሚያሻሽል ተስፋ ያደርጋል” ብሏል። ኤጀንሲው በመቀጠል ይህ የእርቅ ስምምነት “ግጭቱን ለመፍታት መንገድ ይከፍታል” የሚል እምነት እንዳለው ገልጿል።
ህወሓት እጅ ለመስጠት ፍላጎት እንዳለው በመግለፅ፤ የፌደራል መንግስት ለሰላምና ለሰብአዊ እርዳታ ያለው ቁርጠኝነት ላይ ግን ስጋት እንዳለው ገልጿል። ህወሓት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ቃላቸውን ጠብቀው ወደ ትግራይ ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦትን ለማመቻቸት ተጨባጭ የሆኑ እርምጃዎችን እንዲወስዱ ማሳሰቡን ለ AFP በላከው መግለጫ አስታውቋል።
መንግስት ሰላም የማስፈን ፈቃደኝነቱን ለማሳየት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ ከአዲስ አበባ ወደ ትግራይ ዋና ከተማ መቀሌ በየቀኑ የሚደረጉ የአውሮፕላን በረራዎችን መፍቀዱ ነው። ቱርክንና አሜሪካን ጨምሮ በርካታ የአለም ሀገራት በፈደራል መንግስቱ ሰላምን ለማምጣት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን አበረታተዋል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ጄ. ብሊንከን በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ “የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ያወጣውን ላልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ እርቅ ማወጁን አሜሪካ በደስታ የተቀበለችህውና የምትደግፈው ነው” ብለዋል። አክለውም “ጦርነቱን የማቆም ቁርጠኝነት በትግራይ ውስጥ ለሚኖሩ ህዝቦች እና ለሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች እና ማህበረሰቦች ሰብአዊ እርዳታን ለማስቀጠል ወሳኝ እርምጃ ሊሆን ይገባል።” ብለዋል።
ህወሓት የፌደራል መንግስት ቃሉን እንዲያከብር እየጠየቀ ሲሆን የፌደራል መንግስት ደግሞ በአፋር እና በትግራይ አዋሳኝ ቁልፍ ቦታዎች ላይ የሰፈሩት የትግራይ ተወላጅ ሃይሎች እንዲወጡ እየጠየቀ ይገኛል።
ይሁን እንጂ ከነዚህ ሁለት ወገኖች በተጨምሪ ሰላምን ለማስፈን አስፈላጊ የሆኑ ሊሎች አካላት አሉ። በሁለቱ ወገኖች ብቻ የሚደረገው እርቅ ስኬታማ ቢሆን እንኳን ሰላም ለመፍጠር በሚደረጉ ውይይቶች ውስጥ ያሉ ሌሎች አካላት አሁንም ጦርነቱን ለምቆም ዝግጁ ላይሆኑ ይችላሉ።
በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ውስጥ አሁንም የመንበረ ስልጣኑን መብት የሚጠይቅ መንግስት “ኦነግ ሻኔ” ብሎ የሰየመው ቡድን መኖሩ ይታወቃል። ለመዋጥ የሚጎመዝዘው ከህወሓት ጋር እርቅ የመፍጠር ጉዳይ የሁለት አመት ጦርነት መቋጫ ሊሆን ቢችልም የአዲስ ተቃዋሚዎች መጀመሪያ ሊሆን ይችላል።