Horn Magazine
Wednesday, May 14, 2025
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
Horn Magazine
No Result
View All Result

Home » አለም አቀፍ ተከፋይ ጦረኞች ዩክሬንን ለማገዝ ፍቃደኝነታቸውን አሳዩ!

አለም አቀፍ ተከፋይ ጦረኞች ዩክሬንን ለማገዝ ፍቃደኝነታቸውን አሳዩ!

አለም አቀፍ ህግ የተከፋይ ጦረኞች ተሳትፎን ቢከለክልም በጎ ፈቃደኞች ወደ ዩክሬን እየገቡ ነው።

March 24, 2022
in ዓለም
1 min read
Worldwide Mercenaries Seeking to Help Ukraine ዜሌኒስኪ
ShareSharePin

የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በተጀመረ በሶስተኛው ቀን በ የካቲት 20 የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ በአለም ላይ ያሉ በጎ ፍቃደኞች ዩክሬንን በማገዝ የትግል ሜዳውን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበው ነበር። እንደ መደለያም በጎ ፍቃደኞቹ የተሻለ ኑሮ በዩክሬን እንደሚኖራቸው ጠቆም አድርገው አልፈዋል። ይህ ጥሪ 27 አመት በሞላው ናይጄሪያዊው ኦታህ አብርሀም በደንብ ነው የተሰማው። በትዊተር ገፁ ላይም “ልቀላቀላቸው(የዩክሬን ጦረኞችን) እፈልጋለሁ!” ሲል ፅፏል።

አብርሀም የተሻለ ኑሮ እንደሚፈልግ ከመናገሩ ባሻገር ሩሲያ በዩክሬን የምትሸነፍበት እድል አለ የሚል ሀሳብ ያለው ወይም ደግሞ በናይጄሪያ ባለው ህይወቱ ጨለምተኛ የሆነ ይመስላል። ይህም ለጦርነቱ ዝግጁ እንዲሆን ገፍቶታል።

“ጦርነት ነው። የልጆች ጨዋታ እንዳልሆነ አውቃለሁ። ነገር ግን በዩክሬን ወታደር መሆን እዚህ ከመኖር ይሻላል። ምን አልባት ጦርነቱ ካለቀ በኋላ እዛው የምቆይበት እድል ላገኝ እችላለው። በተጨማሪም ጀግና በመሆን ከጠላት ጋር እፋለማለሁ።” ሲል ለ ቢቢሲ ተናግሯል።

የአብርሀምን ሀሳብ በ ኬኒያ ናይሮቢ ተማሪ የሆነው ኪማንዚ ካሾን አስተጋብቷል። “እዚህ ሆኜ ላገኘው የማልችለውን አሪፍ ክፍያ ዩክሬን የምትከፍለኝ ከሆነ ወደዛ ሄጄ ለመዋጋት አላቅማማም።” ብሏል። 

ከ ዜሌንስኪ ጥያቄም ሆነ ከአንዳንድ በጎ ፍቃደኞች ድጋፍ ባሻገር የሌላ ሀገር ጦር ላይ መሳተፍ በብዙ ሀገሮች የሚደገፍ አይደለም። ይሁን እንጂ ዜሌንስኪ እርዳታ ከመጠየቅ አልተወገደም።

ዜሌንስኪ አለም አቀፍ የ ዩክሬን አጋዥ ቡድን ለማቋቋም ጥሪ ሲያቀርብ “የአለም ሰዎች የ ዩክሬን፣ የሰላም እና የዴሞክራሲ ወዳጆች በሙሉ የ ዩክሬን መከላከያን ለመቀላቀል እና ለማገዝ የምትፈልጉ የአውሮፓ እና የአለም ህዝቦች ወደዚህ መታችሁ ከ ዩክሬናውያን ጎን በመሆን ከጦር ወንጀለኛ ሩስያውያን ጋር መታገል ትችላላችሁ።” ብሏል።

በተጨማሪ የ ዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ተመሳሳይ ጥሪን አድግረዋል። “ዩክሬንንም ሆነ አለም አቀፍ ህግን ለመጠበቅ ፍቃደኛ የሆኑ የውጭ ዜጎች በ የሀገራችሁ የሚገኝ የዩክሬን የዲፕሎማሲ ተቋማትን እንድታናግሩ እጋብዛችኋለሁ። ሂትለርን በጋራ እንዳሸነፍነው ሁሉ ፑቲንንም እናሸንፈዋለን።” ሲሉ በትዊተር ገፃቸው ላይ አጋርተዋል።

የዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስተር የበጎ ፍቃደኞች የሚመዘገቡበት መካነ-ድር ቢያዘጋጅም በአለም ላይ በሚገኝ ሀገሮች ላይ በዛ ያለ ተቀባይነትን ያገኘ አይመስልም። አሜሪካ እና ካናዳን ጨምሮ ሌሎች ሀገራትም ዜጎቻቸው ሀገራቸው በቀጥታ ከተሳተፈችበት ጦርነት ውጪ በሌላ ሀገር የጦር ጉዳይ ላይ እንዳይሳተፉ የሚከለክል ህግ አላቸው። 

በተጨማሪም የአውሮፓ ሀገሮች ተመሳሳይ ህግ አላቸው። ጀርመን በጦርነቱ ላይ መሳተፍ የአለም አቀፍ ህግን የሚፃረር መሆኑን በመጥቀስ ዜጎችዋ በጦርነቱ እንዳይሳተፍ እና ከተሳተፉም እርምጃ እንደሚወስድባቸው አስጠንቅቃለች። 

አፍሪካውያን በጦርነቱ ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም ሀገሮቻቸው ግን ተሳትፎውን በመኮነን ላይ ይገኛሉ። የ ናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ቃል አቀባይ ፍራንሲሳካ ናይጄሪያ ዜጎቿ በበጎ ፍቃደኝነት ተከፋይ ጦረኞች ሆነው እንዲያገለግሉ እንደማትፈቅድ ተናግረዋል። “ናይጄሪያ በየትኛውም የአለም ክፍል ተከፋይ ጦረኞች በጦርነት መሳተፋቸውን አትደግፍም። ምልመላውንም አትታገስም።” ብለዋል። 

አልጄሪያም በበኩሏ የዩክሬን መንግስት ዜጎችዋን ለመመልመል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በብርቱ ተቃውማለች። በተጨማሪም የሴኔጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር በሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሚገኘው የዩክሬን ኢምባሲ ሴኔጋላውያን ወደ ዩክሬን በማቅናት ጦርነቱን እንዲሳተፍ በመጠየቁ መገረማቸውን ገልፀዋል።

የዩክሬን ኢምባሲ የለቀቀው የፌስቡክ ፖስት ቢጠፋ ይፋዊ በሆነ መግለጫ የሴኔጋል መንግስት ድርጊቱን አውግዟል። ዜጎቹ በሴኔጋል ምድር በውጭ ሀገር ተከፋይ የሚሆኑ ጦረኞችን ከመመልመል እንዲታቀቡም አስጠንቅቋል።

ይሁን እንጂ እነዚህን ማስጠንቀቅያዎች ችላ ብለው በጎ ፍቃደኞችን ሲመዘግቡ የቆዩት የ ዩክሬን ባለስልጣናት ከ 20 ሺህ በላይ በጎ ፍቃደኞች ከ 52 ሀገራት እንደተመዘገቡ ተናግረዋል። ይህ ቁጥር ህጋዊ የሆነውን መስመር ሳይከተሉ ዩክሬናውያኑን ለማገዝ የገቡ ሰዎችን አይጨምርም።

ዩክሬን 20 ሺህ በጎ ፈቃደኞች እንደተመዘገቡ ስትናገር ሩሲያ በበኩሏ 16 ሺህ ሰዎች እናግዛችሁ የሚል ጥሪን እንዳቀረቡ ገልፃለች በዛ ያሉት በጎ ፈቃደኞችም ከ መሀከለኛው ምስራቅ የመጡ ናቸው። በጎ ፍቃደኞቹ በጦርነቱ እንዲሳተፉም ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፍቃዳቸውን ሰተዋል። ከዚህ ባሻገር ፕሬዝዳንቱ በዩክሬን በኩል በጦርነቱ ላይ ተከፋይ ተዋጊዎች መሳተፋቸው እና ምዕራባውያኑ ለ ዩክሬን እየሰጡ ያሉት ድጋፍ ከአለም አቀፍ ህግ በተቃርኖ የቆመ ነው ሲሉ ተችተዋል። 

Related Posts

Dr. Tedros
ዓለም

አለም ከዩክሬን ጋር እያዘነ ባለበት ጊዜ የአለም የጤና ድርጅት ዋና ሃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በ አፍሪካ ስላለው ግጭት መከሩ

April 25, 2022
rubel ሩብል
ዓለም

የራሺያ ሩብል የተለያዩ ማዕቀቦች ቢጣሉበትም በአጭር ግዜ አንሰራራ!

April 19, 2022
Israel Attempts to Ban Ethiopians for Easter እስራኤል
ዓለም

እስራኤል የኢትዮጲያውያን ጉዞ እግድ አነሳች!

April 15, 2022
Ethiopian Government Declares Humanitarian Truce with Tigray - የኢትዮጵያ
ዓለም

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት የሰብአዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆን ከ ህወሀት ጋር የተኩስ አቁም አወጀ!

April 4, 2022
Russia Ukraine War threatens world food supply
ዓለም

የዩክሬን ጦርነት የአለም ምግብ አቅርቦት ላይ ስጋት ጣለ!

March 21, 2022
African Nations Divided on the Russia-Ukraine Crisis
ዓለም

አፍሪካውያን በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ላይ የተለያየ አቋም አሳዩ!

March 23, 2022

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

POPULAR POST

No Content Available
Load More

RECENT POST

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

March 8, 2023
Ethiopian

New Direct Flights from Atlanta to Ethiopia

January 25, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

January 6, 2023
Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

December 19, 2022
Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

December 13, 2022
Horn Magazine

The Horn Magazine is a U.S. based, online magazine that serves to provide meaningful articles on a variety of subjects that impact your daily lives.

Contact info@hornmagazine.com

CATEGORIES

English                Amharic                 Somali 
National                ብሔራዊ                    Qaran
World                     ዓለም                      Adduunka
Sports                    ስፖርት                   Ciyaaraha
Finance                  ፋይናንስ                 Maaliyadda
Health                    ጤና                       Caafimaadka
Education              ትምህርት                Waxbarasho
Entertainment      መዝናኛ                   Madadaalo

SUBSCRIBE NEWSLETTER

Loading
  • About
  • Advertise
  • Privacy & Policy
  • Contact

© 2021 Horn Magazine

No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health

© 2021 Horn Magazine