ዘይነብ መሀመድ በሚኒሶታ ሴኔት ለመወዳደር በእድሜ በጣም ትንሽ ስለመሆኗ የተሰጣትን ምክር ውድቅ ማድረጓ ውጤት አስገኝቶላታል። ታድያ በውጮቹ ጥር 3 ቃለ መሃላ ፈጽማ የሀሴት ፈገግታዋን ማቆም አልቻለችም።
በኢኒስታግራም ገጿ ላይ “ዛሬ ለእኔ በጣም አስደሳች ቀን ነበር። ለምንወደው የደቡብ ሚኒያፖሊስ ንግግር ለማድረግ ጓጉቻለሁ። በእኔ ላይ እምነት ስላሳደራችሁም አመሰግናለሁ።” በማለት ፅፋለች።
ዘይነብ በቤተሰቦቿ፣ በኢማሟ እና በሌሎች ደጋፊዎቿ ተከባለች። የኤልቲ ገዥ ፔጊ ፍላናጋን እንዳሉት ይህ “ወደፊት እንደ ሚኒሶታ ላሉ ሀገራት የሚወሰድ እርምጃ ነው” ብለዋል። ምክንያቱ ደግሞ ከሚኒሶታ ነዋሪዎች ይልቅ የሚኒሶታ የሕግ አውጪነት የተቆጣጠሩት ነጮች በመሆናቸው ነው።
ከዘር ልዩነት በተጨማሪ ዘይነብ በሴቶች፣ ሙስሊሞች እና ጄነ-ዜድ በሴኔት ውስጥ ያለውን ልዩነት እያጠበበች ነው። ከተለያየ ዓይነት ዳራ ለመጡ ብዙ ፖለቲከኞች አዲስ የተስፋ ብርሃን ልትሆን ትችላለች።
ወይዘሮ ዘይነብ ወጣቱ በፖለቲካ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት ታምናለች። “ሁላችንም በህብረት እየገለፅን ነው ምክንያቱም ሰዎች ትክክለኛውን ነገር እንዲያደርጉ መጠበቅ በጣም ስለሰለቸን ስልጣንን በእጃችን እያደረግን ነው” ስትል ዘይነብ ተናግራለች።
ዘይነብ ለግዛቱ ሴኔት እጩነቷን ስታሳውቅ ገና 24 አመቷ ነበር። እና አንድ አመት ሳይሞላት ባለፈው ህዳር ታሪካዊ ድልዋን እያከበረች ነበር።
ዘይናብ ለመፍታት ካቀደቻቸው ጉዳዮች መካከል የስነ ተዋልዶ መብት፣ የመኖሪያ ቤት እና የኢኮኖሚ ልማት ይገኙበታል። በተጨማሪም ሁሉም ሰው የመንጃ ፈቃድ ማግኘት እንዲችል አያደረገች ነው። አሁን ላይ ህጋዊ የስደት ማረጋገጫ የሌለው ግለሰብ የመንጃ ፍቃድ ሊኖረው አይችልም።
ዘይነብ የሶማሊያ ተወላጅ ስትሆን ወደ ሚኒሶታ የሄደችው በ9 ዓመቷ ነው። በሚኒሶታ የመጀመሪያዋ ሙስሊም ሴት ሴናተር ነች። አሁን በሴኔት ውስጥ የመጀመሪያው ሶማሌ አሜሪካዊ ከነበረውን ሴናተር ኦማር ፋቲህን ተቀላቅላለች።