Horn Magazine
Wednesday, May 14, 2025
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health
No Result
View All Result
Horn Magazine
No Result
View All Result

Home » አብይ አህመድ ከህወሓት ጋር እንደራደራለን አሉ?

አብይ አህመድ ከህወሓት ጋር እንደራደራለን አሉ?

March 23, 2022
in ዓለም
Civil War - አብይ አህመድ
ShareSharePin

በታህሳስ 2 ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ በትዊተር የማህበረሰብ ትስስር ገፃቸው ላይ በአለም ዙርያ ለሚገኙ አንድ ሚሊየን ኢትዮጵያውያን በጥር 7 ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ ግብዣቸውን አስተላልፈዋል። ይህ ግብዣ የሰላም ተስፋን ያነገበ እና የዲያስፖራው ማህበረሰብም ለእናት ሀገሩ አለኝታነቱን እንዲያሳይ ያለመ ቢሆንም ወደ ሀገር ከገቡ በኋላ የተከሰቱ አንዳንድ ጉዳዮች መለምለም ጀምሮ የነበረውን ተስፋ ማጨለማቸው አልቀረም።

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ በፌደራል መንግስት እና በህውሓት መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ድርድር እንደሚደረግ እንደተናገሩ በአሜሪካ የኢትዮጵያ ህዝብ ጉዳዮች ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መስፍን ተገኑ ተናግረዋል። አቶ መስፍን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር ሲጠቅሱ “ ምክንያትያዊ የሆነ የሀገሪቱን አንድነት ጥቅም የሚያስቀድም ድርድር ይኖራል።” ብለዋል። በሌላ በኩል የህውሓት መሪ የሆኑት ዶ/ር ደብረጺዮን ከቢቢሲ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ቀጥተኛ ያልሆነ ውይይት ጀምረናል ብለዋል።

የቢቢሲ አፍሪካ ባልደረባ የሆነው ዊል ሮዝ በትዊተር ገፁ ላይ እንዳሰፈረው “የህውሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፂዮን ገብረሚካኤል ለቢቢሲ ከአዲስ አበባ መንግስት ጋር መነጋገር መጀመራቸውን ገልፀዋል። በሶስተኛ አካል እየተደረገ ያለው ይህ ድርድር ተስፋ ሰጪ ቢሆንም የተሻለ ፍሬ እስኪያፈራ በመጠባበቅ ላይ ነን።” ብለዋል።

ከዚህ ድርድር ጀርባ ማን እንዳለ እና በማን እየተመራ እንደሆነ ግልፅ አይደለም። ሆኖም አንዳንድ እየተናፈሱ እንዳሉ መረጃዎች ከሆነ አሜሪካ ወይም ኬንያ ሊሆኑ ይችላሉ። ይህ የድርድር ወሬ እየተናፈሰ ባለበት በዚህ ወቅት በአማራ እና አፋር ክልሎች የመልሶ ግንባታ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው ይሁን እንጂ በ ትግራይ የሚኖሩ 6 ሚሊየን ነዋሪዎች ዛሬ ድረስ ከሁለንተናዊ እንቅስቃስያቸው ታግደዋል። ይህንን ሁኔታም ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረ እየሱስ “ገሃነም” ሲሉ ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የፌደራል መንግስት በሰላማዊ ድርድሩ ላይ ፅኑ መሆኑን ለማሳየት በርካታ እርምጃዎችን ወስደዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ “የህዝቡ ስቃይ እንዲያበቃ ለማድረግ የሚያስችለውን የትኛውንም እንቅስቃሴ እናደርጋለን!” ብለዋል ሲሉ አቶ መስፍን ተገኑ ተናግረዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ በትግራይ ክልል የነበረውን የኔትዎርክ አውታር ወደነበረበት ለመመለስ እየሰሩ መሆናቸውን እና ይህን ለማሳካትም 7 ቢሊዮን ብር በጀት መድበው እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ የህወሓት መሪዎችን ጨምሮ በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ከእስር ተፈትተዋል ይህ በህዝቡ ዘንድ የተለያየ ስሜትን ፈጥሯል።

የድርድር ወሬ እየተነሳ ባለበት እና በመንግስት በኩልም ለድርድሩ መሳካት የተደረጉ የሚመስሉ እርምጃዎች ባሉበት በዚህ ወቅት ህውሓት የድርድሩን ተፈፃሚነት ጥያቄ ውስጥ እንዲከት በሚያስገድድ መልኩ በአፋር ክልል ወታደራዊ ጥቃት ፈጽሟል። ለትግራይ አዋሳኝ በሆነችው የአባላ ከተማ ነዋሪዎች ከጥር 14 ጀምሮ በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ የተኩስ እሩምታ እንደነበር መስክረዋል። ተኩሱ ትምህርት ቤቶች፣ መስጂዶች እና መኖሪያ ቤቶችን አውድሟል። ከዚህም አልፎ ወደ ትግራይ የሚገቡ የእርዳታ መንገዶች እንዲዘጉ ምክንያት ሆኗል።

በጥቃቱ ወቅት በቦታው እንደነበሩ የሚናገሩት የአባላ ከተማ ነዋሪ ኡመር አሊ “የህውሃት ወታደሮች ከተራራ ላይ ሆነው ሲተኩሱብን ነበር። ይህ ጥቃት የአፋር ክልል ልዩ ሀይሎችን አዳክሟል። ይህን መዳከም ተከትሎ የህውሀት ሀይል ወደ ከተማዋ እየተቃረበ በመምጣቱ የአፋር መንግስት የከተማው ነዋሪዎች ጦርነቱን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል። የታጠቁ የአካባቢው ነዋሪዎች ጦርነቱን ሲቀላቀሉ የህውሀት ወታደሮቹ ወደ ኋላ አፈግፍገዋል።” ሲል ገልጿል።

በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራው የኢትዮጲያ ብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ከመከላከያ ሰራዊት ጋር የህወሓትን ትንኮሳ አስመልክቶ ተወያይቷል። የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተመስገን ጥሩነህ የመከላከያ ሰራዊት እርምጃ እንዲወስድ አቅጣጫ መቀመጡን ቢናገሩም ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በ ድርድሩ ጉዳይ ተስፋ ሰጪ ጭላንጭል የታየ ቢመስልም በአፋር የተደረገው ጥቃት ግን ለስኬቱ እንቅፋት ሳይሆን አይቀርም። ለጥቃቱ መከላከያ ምንም አይነት አፀፋዊ እርምጃን አልወሰደም የፌደራል መንግስቱም ቢሆን ድርድሩን በማስመልከት የትኛውንም ይፋዊ መግለጫ አልሰጠም።

Related Posts

Dr. Tedros
ዓለም

አለም ከዩክሬን ጋር እያዘነ ባለበት ጊዜ የአለም የጤና ድርጅት ዋና ሃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በ አፍሪካ ስላለው ግጭት መከሩ

April 25, 2022
rubel ሩብል
ዓለም

የራሺያ ሩብል የተለያዩ ማዕቀቦች ቢጣሉበትም በአጭር ግዜ አንሰራራ!

April 19, 2022
Israel Attempts to Ban Ethiopians for Easter እስራኤል
ዓለም

እስራኤል የኢትዮጲያውያን ጉዞ እግድ አነሳች!

April 15, 2022
Ethiopian Government Declares Humanitarian Truce with Tigray - የኢትዮጵያ
ዓለም

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት የሰብአዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆን ከ ህወሀት ጋር የተኩስ አቁም አወጀ!

April 4, 2022
Worldwide Mercenaries Seeking to Help Ukraine ዜሌኒስኪ
ዓለም

አለም አቀፍ ተከፋይ ጦረኞች ዩክሬንን ለማገዝ ፍቃደኝነታቸውን አሳዩ!

March 24, 2022
Russia Ukraine War threatens world food supply
ዓለም

የዩክሬን ጦርነት የአለም ምግብ አቅርቦት ላይ ስጋት ጣለ!

March 21, 2022

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

POPULAR POST

No Content Available
Load More

RECENT POST

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

Jamal Osman Seeks Minneapolis City Council Re-Election

March 8, 2023
Ethiopian

New Direct Flights from Atlanta to Ethiopia

January 25, 2023
Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

Zaynab Mohamed Sworn into the Minnesota Senate

January 6, 2023
Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

Last African Nation Standing in the World Cup Falls to France

December 19, 2022
Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

Cameroon Defeats Brazil but Fail to Qualify for the Next Round

December 13, 2022
Horn Magazine

The Horn Magazine is a U.S. based, online magazine that serves to provide meaningful articles on a variety of subjects that impact your daily lives.

Contact info@hornmagazine.com

CATEGORIES

English                Amharic                 Somali 
National                ብሔራዊ                    Qaran
World                     ዓለም                      Adduunka
Sports                    ስፖርት                   Ciyaaraha
Finance                  ፋይናንስ                 Maaliyadda
Health                    ጤና                       Caafimaadka
Education              ትምህርት                Waxbarasho
Entertainment      መዝናኛ                   Madadaalo

SUBSCRIBE NEWSLETTER

Loading
  • About
  • Advertise
  • Privacy & Policy
  • Contact

© 2021 Horn Magazine

No Result
View All Result
  • Home
  • National
  • World
  • Finance
  • Community News
  • Education
  • Sports
  • Health

© 2021 Horn Magazine